Haramaya University

Haramaya University Haramaya University is one of the oldest universities in Ethiopia. It is located 5 km from Haramaya, welcome
(1)

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የ2018 ዓ/ም እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ትምህርት መርሃ-ግብር በሐረማያ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሰሯቸውን ስራዎች አስመረቁተማሪዎቹ ...
28/12/2025

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የ2018 ዓ/ም እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ትምህርት መርሃ-ግብር በሐረማያ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሰሯቸውን ስራዎች አስመረቁ

ተማሪዎቹ በገዳ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በ02 ቀበሌ ጽህፈት ቤት ግቢ ውስጥ የሰሯቸው ሥራዎች ለምርቃት በቅተዋል።


በገዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ሴት ተማሪዎች በወር አበባ ጊዜ የሚያርፉበትና የሚታጠቡበት ክፍሎች እና ቀበሌ 02 የሚገኝ አገልግሎት መስጠት ያቆመ የህዝብ መጸዳጃ ቤትን አድሶ ወደ አገልግሎት የመመለስ ስራ ተሰርቷል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ መምህር ዶ/ር ፈቲያ መሐመድ አብዱሌ ፕሮጀክቶቹን በመረቁበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ቤቱ ሴት ተማሪዎች በወር አበባ ወቅት ክፍል ውስጥ መቀመጥ ስለሚቸገሩ ከትምህር የሚቀሩበት አጋጣሚ ስለሚኖር በትምህርታቸው ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽዕኖ የሚቅፕንስ ስራ ተሰርቷል፡፡

ሴት ተማሪዎች ሴትነታቸው ሳይበግራቸው ትምህርታቸውን በርትተው በመማርና የእነሱን አርዓያነት በመከተል ጥሩ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችሉ ዶክተር ፈቲያ አብራርተዋል፡፡

የገዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አህመድ መሃመድ እንደገለጹት ተማሪዎቻቸው በወር አበባ ወቅት ማረፊያ ክፍል ስለሌላቸው ፈቃድ ወስደው ወደ ቤታቸው እንደሚሄዱና ይህም በትምህርታቸው ላይ ተጽዕኖ እያሳደረባቸው እንደነበርና በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የተሰራው ስራ ችግሩን እንደሚቀርፍላቸው ተናግረዋል፡፡

የተግባር ተኮር ትምህርት ተማሪዎች የሐረማያ ከተማ ቡድን ሪፖርት አቅራቢ ተማሪት ያብስራ አብነት እንደገለጸችው በሐረማያ ከተማ የተሰሩት ሁለት ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ ስራዎች ናቸው ብላለች፡፡

ተማሪዎቹ በቡድን ባደረጉት ጥረት ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት ባሰባሰቡት የገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ ለሁለቱ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ የሰው ጉልበትን ጨምሮ አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር የሚገመት ገንዘብ ለፕሮጀክቶቹ ማስፈጸሚያ እንዳወጡ ተናግራለች፡፡

በተግባር ተኮር ትምህርት ከንድፈ ሃሳብ በተጨማሪ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን እውነታ ተረድተው ችግሮቹን ለይቶ በማስተባበር መፍታት እንደሚቻል፣ የቡድን ስራን ጠቀሜታ እና እውቀትን ወደ ተግባር ቀይሮ ለማህበረሰቡ ጠቃሚ ስራ መስራት እንደሚቻል እንደተማሩበት ተማሪት ሰብሪና አባስ እና ሌሎች ተማሪዎችም ገልጸዋል፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈር፦ ሲሳይ ዋቄ

Haramaya University Supports Deborah Foundation’s Dairy Farming InitiativeHaramaya University has extended institutional...
28/12/2025

Haramaya University Supports Deborah Foundation’s Dairy Farming Initiative

Haramaya University has extended institutional support to the Deborah Foundation in its effort to establish a dairy farming project aimed at enhancing sustainability and nutrition.

The Deborah Foundation is a non-profit organization committed to promoting inclusion, dignity, and quality of life for children with Down syndrome and other intellectual disabilities.

A delegation from Haramaya University, led by Dr. Ketema Bekele, Director of University Enterprise Development, paid a courtesy visit to the Foundation on 19th December 2025 to strengthen collaborative engagement.

The delegation was formally received by the Founder and Chairperson of the Deborah Foundation, Mr. Abadulla Gemeda, who also guided the visit.

As part of the Foundation’s plan to achieve self-sufficiency for its forthcoming school feeding program, a dairy farm initiative has been launched. In support of this effort, Haramaya University donated five dairy cows valued at 1.25 million Birr.

The donation was officially handed over to Mr. Abadulla Gemeda, who expressed deep appreciation for the University’s sustained commitment. He noted that the support plays a significant role in advancing the Foundation’s mission and long-term vision.

“This generous contribution from Haramaya University represents a transformative milestone for our Foundation,” Mr. Abadulla stated, emphasizing its impact on community-based development and social welfare.

In recognition of the University’s contribution, Mr. Abadulla Gemeda presented an official certificate of appreciation to Haramaya University, acknowledging its outstanding role in supporting inclusive development initiatives.

Haramaya University Public & International Relations Directorate

የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያ ዝግጅትን ለመገምገም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲካሄድ የነበረው አውደ ጥናት ተጠናቀቀበያዝነው ዓመት የመጀመሪያ ዕትም የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያን ለማውጣት ዝግጅት እየተጠ...
28/12/2025

የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያ ዝግጅትን ለመገምገም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲካሄድ የነበረው አውደ ጥናት ተጠናቀቀ

በያዝነው ዓመት የመጀመሪያ ዕትም የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያን ለማውጣት ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገልጿል።


የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር ያሰራቸውን 39 ጥናታዊ ፅሁፎች ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ቀርበው ተገምግመዋል።

በገዳ ስርአት ኢሬቻ ላይ መሰረት ያደረገ ኢንሳይክሎፔዲያ መፅሐፍ ለማዘጋጀት በኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት አስተባባሪነት የተሰሩት የጥናት ውጤቶች ለአባ ገዳዎች ፧ ለአፋን ኦሮሞ ቋንቋና ታሪክ ተመራማሪዎች ፧ አስተማሪዎችና ተማሪዎች በተገኙበት ቀርበው ለሶስት ቀን ግምገማ ተካሂዶ የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡ ታውቋል።

የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት እንዳብራሩት ኢኒስቲትዩቱ የአፋን ኦሮሞን ባህል ታሪክና ስነጥበብ የኦሮሞን ህዝብ በሚመጥን መልኩ አጥንቶ ህዝቡ ያለውን እውቀት በተለያዩ ቋንቋዎች ለትውልድ ለማስተላለፍ አላማው አድርጎ በ2014 ዓ/ም የተቋቋመ መሆኑን አብራርተዋል ።

ገዳ የዲሞክራሲ ስርአት ምንጭ በመሆኑ ለአፍሪካና ለአለም ተምሳሌት በሚሆን ባህላዊ የአስተዳደራዊ ስርዓት ኦሮሞ ሲተዳደርበት ችግሮችን በውይይት የሚፈታ ፣ ሰላም የሚሰብክ ፣ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በውስጡ የያዘ በመሆኑ ይህን ስርዓት በዓለም ላይ እየተፈጠሩ ላሉ ችግሮች መፍትሔ እንዲሆን ጥናቶች እየተከናወኑ ኢንሳይክሎፒዲያ መፅሐፍ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን እየተሰራ መሆኑን አቶ ዝናቡ ገልፀዋል።

በመድረኩም የተሰሩ የጥናት ውጤቶች መገምገማቸውን ፣ በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎችን አቅጣጫዎችም በመድረኩ መጠቆማቸውንና በዚሁ መሰረት ኢኒስቲትዩቱ ኢንሳይክሎፒዲያውን አሳትሞ ለማህበረሰቡ እንደሚያከፋፍል አቶ ዝናቡ አብራርተዋል።

በያዝነው ዓመት የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያን ለማሳተም ኢኒስቲትዩቱ ከ60 እስከ 80 የሚሆኑ ርዕሶችን መርጦ በራሱ ተመራማሪዎችና ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆንም ጥናትና ምርምሮችን እየሰራ ሲሆን ባለፉት ሶስት ቀናትም በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ 39 ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበው ገንቢ ግበአት እንደተገኘበት ገልፀዋል።

በኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት የቋንቋና ባህል ተመራማሪ ወይዘሮ ድርቤ ቀነአ በአቴቴ ፣ አብዳሪና ፋሩ ኢሬቻ ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን ኢሬቻ ላይ ያተኮሩ ቃላቶችን መሰረት አድርገው ባቀረቡት ጥናት ላይ በርካታ ግብአት የሚሆኑ ሀሳቦች አግኝተናል ብለዋል።

ከወራቶች በፊት በተመሳሳይ በጅማ ዩኒቨርሲቲም አስራ አንድ በአጠቃላይ እስከ አሁን ከ50 የሚበልጡ ጥናታዊ ፅሁፎች ተገምግሞ ጠቃሚ ግብአቶች መገኘቱን የባህል ተመራማሪዋ ጨምረው ገልፀዋል።

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ኢማና በየነ በተለያዩ ሶስት ርዕሶች ጀማ ፣ ኪላ ና አርዳ ጂላ በተሰኙ ርዕሶች ላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን ያቀረቡ ሲሆን በመድረኩም ላይ ገንቢ ሀሳቦች እንደተሰጣቸው ገልፀዋል።

ኢሬቻ ዘርፈ ብዙ ጠቃሚ እሴቶችን በውስጡ የያዘ ከገዳ ስርአት ውስጥ የሚመዘዝ መሆኑን የተናገሩት በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያ ዝግጅት ጥናታዊ ፅሁፍ ግምገማ መድረክ አስተባባሪ ዶክተር ዳንኤል በሊና እንደተናገሩት ኢሬቻ መጠያየቅን ፣ መመካከርን ፣ የህግ አዋጆችንም በውስጡ የያዘ ጥልቅ የአስተሳሰብ ስርአትን ያቀፈ በመሆኑ ይህን ብርቅዬ ዕሴት ለትውልድ ለማስተላለፍ የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዮት ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፣ ጅማ ፣ አዲስ አበባና አርሲ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር እየሰራ ያለው ስራ ሀገራዊ ዕውቀትን ለትውልድ ማስተላለፍ በመሆኑ ሁሉም የራሱን አስተዋፅዎ ማበርከት አለበት ብለዋል።

የአፍረን ቀሎ አባሐዋስ አህመዲን ሙክታር እንዳሉት የገዳ ስርዓት በዩኔስኮ እንደተመዘገበ ሁሉ ኢሬቻንም ለማስመዝገብ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንና የተለያዩ ቃላቶችን በኢንሳይክሎፒዲያ መዝግቦ ለማሳተም በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይትና ምክክር መደረጉንና የገዳ ስረአት እሴቶችን በጠበቀ መልኩ ለትውልድ እንዲሻገር የሚያስችል በመሰራቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል።

በያዝነው የ2018 ዓመት የመጀመሪያውን ዕትም የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያ ለማውጣት የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።

ዘጋቢዎች፦ ሀብታሙ ኃ/ጊዮርጊስና ደሞዝ ያዕቆብ
ፎቶግራፈር፦ ቴዎድሮስ ሊሻን

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በባቢሌ ከተማ የሰሯቸው የልማት ስራዎች ተመረቁየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የቡድን ተግባር ተኮር ልምምድ ስልጠና በትምህርት ስርዓት ውስጥ ተካቶ መሰጠቱ ብቁ የጤና ባለሙያዎችንና ...
28/12/2025

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በባቢሌ ከተማ የሰሯቸው የልማት ስራዎች ተመረቁ

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የቡድን ተግባር ተኮር ልምምድ ስልጠና በትምህርት ስርዓት ውስጥ ተካቶ መሰጠቱ ብቁ የጤና ባለሙያዎችንና አመራሮችን ለማፍራት እገዛ እያደረገ መሆኑ ተገለፀ።

በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ባቢሌ ወረዳ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በቡድን ተግባር ተኮር ልምምዳቸው የማህበረሰቡን ችግሮች መፍታት ያስችላል ያሏቸውን የልማት ስራዎች አጠናቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል ።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ መሀመድ ባስተላለፉት መልእክት በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ወደ ህብረተሰቡ መላካቸው አካባቢያቸውን ተረድተው በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን እውቀት እና ክህሎት በመጠቀም ችግር ፈቺ የልማት ስራዎችን መስራታቸው ጠቁመው ዩኒቨርስቲው የቡድን ተግባር ተኮር ትምህርት መርሀግብር በስርዓተ ትምህርት ውስጥ ተካቶ መሰጠቱ ለጤናው ዘርፍ ብቁ ባለሙያዎች እና አመራሮችን ማበርከት አስችሏል ብለዋል።

በዚህም በባቢሌ ከተማ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ያከናወኑት የልማት ስራዎች ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

ፕሮግራሙ በኮሌጁ የተለያዩ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ስብጥር ያለው ቡድን ሲሆን በተመደቡበት አካባቢ የጤና ችግሮችን በዳሰሳ ጥናት ለይተው እውቀትና ክህሎታቸውን ተጠቅመው የአካባቢውን ማህበረሰብ እና ተቋማትን በማስተባበር ችግር ፈቺ የልማት ስራዎችን ማከናወን የሚያስችል መሆኑንና የታለመለት አላማን ማሳካቱን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የቡድን ተግባር ተኮር ስልጠና መርሀግብር አስተባባሪ አቶ ካብታሙ ንጉሴ ገልጸዋል።

የባቢሌ ከተማ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ገዛኸኝ በበኩላቸው በዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት የተከናወኑ የወላድ እናቶች ማቆያ እና የማህበረሰብ ፋርማሲ እንዲሁም በዘንድሮው ዓመት የህሙማን ቅድመ ምርመራ ክፍል ቤቶች ግንባታ እና መገልገያ መሳሪያዎችን አሟልተው ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉ ተናግረዋል ።

ይህም ጤና ጣቢያው በአካባቢው ካሉ ስምንት ቀበሌዎች እና አጎራባች ወረዳዎች ለሚመጡ ታካሚዎች እየሰጠ ያለውን አገልግሎት የሚያግዝ እና እውቀትም የተገኘበት ነው ብለዋል።

የባቢሌ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው ልጆቻችን በቆይታቸው ያሳዩን ቅንነትና ትህትና የተላበሰ አገልግሎታቸው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ እንዲሆኑ ያደረገውን ጥረትና ውጤት በተጨባጭ አሳይተውናል ብለዋል።

በቆይታችን የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥሙንም ማህበረሰባችን እየፈተኑ ያሉ የጤና ችግሮች እንደመኖራቸው በአንፃሩ ተቋማት ፣ ባለሙያዎች እና ህብረተሰቡን በማቀናጀት መፍትሔ የማድረግ አቅም መኖሩን መገንዘብ አስችሎናል ሲሉ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በሰጡት አስተያየት ጠቁመዋል።

ዘጋቢ: ታደለ ጥላሁን
ፎቶ ግራፈር : በሐይሉ ግርማ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

27/12/2025
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ በተግባር ተኮር ልምምዳቸው ያስገነቡት የማህበረሰብ ፋርማሲ ተመረቀ ዕጩ ...
27/12/2025

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ በተግባር ተኮር ልምምዳቸው ያስገነቡት የማህበረሰብ ፋርማሲ ተመረቀ

ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በነበራቸው የአምስት ሳምንት የተግባር ተኮር ልምምድ (TTP) ማህበረሰቡ ዘንድ ዘልቀው በመግባት የጤና ችግር ናቸው ብለው የለዮዋቸውን ባለድርሻ አካላትንና የአካባቢውን ህብረተሰብ በማስተባበር የማህበረሰብ ፋርማሲ እና ሌሎች የልማት ስራዎችን አጠናቀው አስመርቀዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሕይወት ፋና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር መሀመድ ኑር አብዱላሂ በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲው የሰጣቸውን ተልእኮ በስኬት እንዲወጡ የሜታ ወረዳ እና የጨለንቆ ከተማ አስተዳደር እና ማህበረሰብ ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

ተማሪዎች የማህበረሰቡን ችግር ይፈታሉ ብለው ያከናወኗቸው የልማት ስራዎች በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጡ በጨለንቆ ከተማ አስተዳደር እና ማህበረሰብ አስፈላጊውን ክትትል መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዘርፎች አካባቢው ላይ እያደረጋቸው ያሉ የልማት ስራዎች በሀገር ደረጃ የአካባቢን ውበት ፣ ፅዳት እና የዜጎችን ጤናና ኑሮን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ያበረከተ መሆኑን ገልፀው ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በአጭር ጊዜ ያከናወኗቸው የልማት ስራዎች ጥሩ ልምድ ያገኘንበት ነው ሲሉ በምስራቅ ሐረርጌ የሜታ ወረዳ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሻፊ አደም ገልፀዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው ተማሪዎች ለብዙ ጊዜ ከመድኃኒት ጋር ተያይዞ እንቸገርበት የነበረን የማህበረሰብ ፋርማሲ አገልግሎትን እንዲሁም የመጠጥ ውሀ ገንብተው በአጭር ጊዜ መፍትሄ በማግኘታችን ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል ።

ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ልምምዳችን ወደ ማህበረሰቡ ከመጣንበት ቀን ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ተንከባክቦ በሰራናቸው ስራዎች ሁሉ ትብብር አድርገውልናል ይህ የማህበረሰባችንን ባህል ወግ እና የአኗኗር ዜዬ ማወቅ አስችሎናል ሲሉ ተናግረዋል።

ዘጋቢ : ታደለ ጥላሁን
ፎቶ ግራፈር :- በሐይሉ ግርማ
ታህሳስ 18/2018 ዓ.ም

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ትምህርት መርሃ-ግብር በቦሮዳ ከተማ የሰሯቸውን ስራዎች አስመረቁ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ...
27/12/2025

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ትምህርት መርሃ-ግብር በቦሮዳ ከተማ የሰሯቸውን ስራዎች አስመረቁ

እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር ትምህርት መርሃ-ግብራቸው ((TTP) Team Trainng Program) ቅድሚያ ተሰጥቶ ሊሰሩ የሚገባቸውን የማህበረሰቡ ችግሮችን ለመለየት ከከተማ መስተዳደሩና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በመለየት የተሰሩ ስራዎች ናቸው የተመረቁት።

በከተማው ጤና ጣቢያ ያለው የወላድ እናቶች ማቆያ ክፍል ፣ የቅድመ-ህክምና መለያ ክፍልና የመጸዳጃ ፍሳሽ ማጠራቀሚያ ችግርን ለማስወገድ የተሰሩ ስራዎች ተመርቀዋል።


የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና የተግባር ተኮር ትምህርት ቡድን አስተባባሪ አቶ ካብታሙ ንጉሴ እንደተናገሩት የኮሌጁ ተማሪዎች ለሚያከናውኑት ተግባር ተኮር ትምህርት በቡድን ተከፋፍለው በዘጠኝ ቦታዎች ተመድበው ሰርተዋል።

በንድፈ ሃሳብ የተማሩትን ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን ችግር በዳሰሳ ጥናት በመለየት መፍትሄ ለመስጠት ገንዘብና ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ ሲሰሩ ቆይተው በቦሮዳ ከተማ የተሰራውን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች የተማሪዎቹ ስራዎች እየተመረቁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አቶ ካብታሙ አያይዘውም የእናቶችና ህጻናት ጤና ጉዳይን ዩኒቨርሲቲያችን በትኩረት እየሰራበት መሆኑንና ተማሪዎቹ ለዚህ ስኬት እንዲበቁ ለተባበሩ አካላት በሙሉ በዩኒቨርሲቲው ስም ምስጋናቸውን ገልጸዋል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አግልግሎት አስተባባሪ አቶ ኢብሳ አሊይ ኡስማን፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህን መሰል ውጤታማ ስራዎችን ሰርተው ማጠናቀቃቸው ተማሪዎቹና ማህበረሱ ተናበውና ተረዳድተው ለሰሩት ስራ አመስግነዋል፡፡

ተማሪዎች ማህበረሰቡ ውስጥ ገብተው አብረው መስራትን በተግባር የሚማሩበት ስለሆነ የኮሌጁ ተግባር ተኮር ትምህርት መርሃ-ግብር ዩኒቨርሲቲው ከሚሰራው የማህበረሰብ አገልግሎት እንደ አንዱ ቆጥሮ 2.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አቶ ኢብሳ ገልጸዋል፡፡

የቦሮዳ ጤና ጣቢያ ምክትል ኃላፊ አቶ መሃመድ ዲኖ ሳፊ እንደተናገሩት በጤና ጣቢያቸው የነበረባቸውን የክፍሎች እጥረት ለረጅም ግዜያት ሲቸገሩበት የቆዩበት የወላድ እናቶች ማቆያ ክፍል ችግር ለመፍታት ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጸው ወደ ስራ በመግባት ሁለት የወላድ እናቶች ማቆያ ክፍሎች ከነማብሰያ ፣ መታጠቢያና መጸዳጃ ክፍሎች ፣ የቅድመ-ህክምና መለያ ክፍልና የመጸዳጃ ፍሳሽ ማጠራቀሚያ ችግሮች በተማሪዎቹ ከፍተኛ ጥረት ስለተቀረፈላቸው የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚያግዛቸው ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

የተግባር ተኮር ትምህርት ተማሪዎች የቦሮዳ ከተማ ቡድን ሪፖርት አቅራቢ ተማሪት ኤዶምገነት አበባው እንደገለጸችው የተሰሩት ሶስት ፕሮጀክቶች ለስኬት የበቁት እስከ አዲስ አበባ ድረስ በመንቀሳቀስ በተማሪዎቸ ያላሰለሰ ጥረት ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት በተገኘ የገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ ሲሆን ለነዚህ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ በአይነትና የሰው ጉልበትን ጨምሮ አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስድስት ሺህ ሶስት መቶ ሃምሳ አንድ (4206351) ብር የሚገመት ገንዘብ እንደወጣበትና ድጋፉን ላደረጉላቸው ግለሰቦችና ተቋማት በተማሪዎቹ ስም ምስጋና አቅርባለች፡፡

ተማሪት ኤዶምገነት አያይዛም በአይነት ከተገኙት ድጋፎች መካከል የአካል ጉዳት ላለባቸው የሚሆን ሁለት ዊልቸር ፣ ለእናቶች ማረፊያ የሚሆን አራት አልጋዎች ፣ ለአንዲት የአካል ጉዳት ያለባቸውን ቤተሰቦቿን ለምታስተዳዳር ሴት ሰላሳ አንድ ሺህ (31150) ብር በማውጣት የችብስ መጥበሻ ማሽን ከነሙሉ እቃዎቹ ድጋፍ ማድረጋቸውንና ወላድ እናቶች በቆይታቸው የሚጠቀሙበት 750 ኪግ የቦቀሎ ዱቄት ፣ 750 ኪግ የስንዴ ዱቄት ፣ 750 ኪግ ሩዝ ፣ 60 ሊትር የምግብ ዘይት ከወርልድ ቪዥን እና 100 ኪግ ስኳር ከፋሚሊ ኸልዝ ኢኒሼቲቭ የተበረከቱት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጻለች፡፡

በዚህ የተግባር ተኮር ትምህርት ከንድፈ ሃሳብ በተጨማሪ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን እውነታ ተረድተው ችግሮቹን ለይቶ በማስተባበር መፍታት እንደሚቻል እንደተማሩበት ተማሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈር፦ ሲሳይ ዋቄ

የኢሬቻ ኢንሳይክሎፔዲያ ለማዘጋጀት የተሰሩ ስራዎችን ለማፅደቅ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ግምገማ እየተካሄደ ነው ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በገዳ ስርዓት የኢሬቻ ኢንሳይክሎፔዲያን ለማዘጋጀት ሲካሄድ በ...
26/12/2025

የኢሬቻ ኢንሳይክሎፔዲያ ለማዘጋጀት የተሰሩ ስራዎችን ለማፅደቅ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ግምገማ እየተካሄደ ነው

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በገዳ ስርዓት የኢሬቻ ኢንሳይክሎፔዲያን ለማዘጋጀት ሲካሄድ በነበረው ጥናት ውጤት ላይ የሚመክር አውደ ጥናት ከትናንት ጀምሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

በአውደ ጥናቱ ላይ አባ ገዳዎች ፣ የታሪክና የቋንቋ ተመራማሪዎች ፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችና እንዲሁም በባህልና ቋንቋ ጥናት ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ሙያተኞች እየተሳተፉ ነው ፡፡

የቋንቋና ባህል ጥናት ስራውን ሐረማያ ፣ አዲስ አበባ ፣ አርሲ እና ጅማ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት የተሳተፉበት እንደሆነ ተገልጿ፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይስሀቅ ዩሱፍ በአውደጥናቱ መክፈቻ ንግግራቸዉ በሐገራችን ትልቁን ቁጥር የያዘው የኦሮምኛ ቋንቋ ቃላቶችና አባባሎች በሚገባው ልክ ባለመጠናታቸው ለትውልድ በሚገባው ልክ ሊተላለፉ ሲገባ ይህ ሳይሆን በመቅረቱ ይን ችግር ለማስቀረት የጥናትና ምርምር ስራው መሰራቱን ተናግረዋል፡፡

ዶክተር ይስሀቅ አክለውም ሀገር በቀል ዕውቀቶች ከሚተላለፉበት መንገድ አንዱ በስነቃልና በተለያዩ ሁነቶች በሚጠቀማቸው ቃላዊ ትውፊቶች በመሆኑ እነዚህን የባህልና የቋንቋ ጥናት ዘርፎች ሳይበረዙ በሚገባ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሐረማያን ጨምሮ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ከኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ጋር በትብብር የጥናት ስራውን ሲያካሂዱ እንደነበር አስታውቀዋል፡፡

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በምስራቅ ሐረርጌ አካባቢ በሚገኙ አካባቢዎች ላይ ሲካሄድ የነበረውን የጥናት ስራ እንዳከናወነና ሌሎቹም ዩኒቨርሲቲዎች በተመደበላቸው አካባቢዎች ያካሄዱትን ጥናት በመድረኩ ላይ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡

ቋንቋ ለአንድ ሀገር እድገት መሰረት በመሆኑ በሚገባው ልክ ጥናት ተደርጎበት ለትውልድ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በማስተላለፍ ለዕድገት እንዲውል ለማድረግ ጥናትና ምርምሮች አስፈላጊ መሆናቸውን ዶክተር ይስሀቅ ጠቁመው በዚህ ዘርፍ የተሰሩ ጥናቶችም በመድረኩ ቀርበው እስከ ነገ ድረስ ግምገማ እንደሚደረግባቸው አስታውቀዋል፡፡

የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት በአሁኑ ጊዜ በኦሮሞ ባህል ፣ ታሪክና የአፋን ኦሮሞ ጥበብ ጋር የተገናኙ ከ40 በላይ ምርምሮችን ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በጋር እየሰራ መሆኑን የኢኒስቲትዩቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት በአውደ ጥናቱ ላይ ተናግረዋል።

የኢሬቻ ኢንሳይክሎፒዲያን ለማዘጋጀት የሚያስችል ጥናቶች በኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ፣ በጅማ ፣ አዲስ አበባ ፣ አርሲና ሐረማያ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራን እየተሰሩ መሆኑን አቶ ዝናቡ ገልጸዋል።

ኢኒስቲትዩቱ የኦሮሞን ባህል፣ ታሪክና የአፋን ኦሮሞ ጥበብን ለትውልድ ማሻገር የሚያስችሉ ምርምሮችን ከ13 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም በራሱ ተመራማሪዎች ከሚሰራው ምርምሮች በተጨማሪ ከ40 በላይ ምርምሮችን ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራ እንደሚገኝ ምክትል ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።

ዘጋቢ ፡- ሐብታሙ ኃ/ጊዮርጊስ
ፎቶግራፈር፡- ቴዎድሮስ ሊሻን
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት

Haramaya University Economics Students Forum Charts Path to Future Careers Amid Growing OpportunitiesHaramaya University...
26/12/2025

Haramaya University Economics Students Forum Charts Path to Future Careers Amid Growing Opportunities

Haramaya University's Economics Students Forum convened a consultative meeting with the Department of Economics to address future career prospects, job market challenges, and opportunities for economics graduates.

The forum brought together deans, faculty, and students from the Business and Economics College to discuss strategies for connecting academia with industry.

Under the theme "The Future Prospects of Economics: Jobs, Opportunities, and Challenges," Professor Alemayehu Geda, a renowned economist from Addis Ababa University, highlighted the high demand for economics professionals in policy-making, finance, global sectors, and textiles. He emphasized that students who integrate modern technology, and artificial intelligence into their studies will become highly competitive candidates in the job market.

"Graduates who adapt their education to contemporary technologies and practical applications will find themselves well-positioned as they enter the workforce," Professor Alemayehu Geda stated.

Dr. Temesgen Keno, a staff member at the College of Business and Economics at Haramaya University, emphasized the importance of networking for professional success in his presentation. He stated, "Building strong professional networks is essential for career advancement. I encourage students to actively engage in research calls, panel discussions, and various forums to improve their communication skills and increase their visibility in the field."

Students expressed their determination to turn academic challenges into career opportunities and affirmed their readiness to compete effectively. Professor Jema Haji from the Agricultural Economics Department at Haramaya University shared his experiences and insights from his professional journey. He encouraged students to take advantage of practical training and mentorship opportunities.

Mr. Milkesa Dejene, the Head of the Department of Economics at HU, emphasized that the department has gathered a team of experienced faculty members with significant practical backgrounds to provide students with real-world knowledge. He stated, "Our goal is to prepare students to understand the specific challenges they may encounter in their studies and careers, and to equip them with the skills necessary to overcome these obstacles."

Elizabeth Alemu, President of the Economics Students Forum, described the meeting as a crucial platform aimed at bridging the gap between academia and industry. "This forum allows students to gain practical insights from industry experts, learn about available opportunities in their field, and strategically prepare for their professional futures," she stated.

The consultative meeting highlighted Haramaya University's commitment to improving graduate employability through focused career guidance and partnerships with industry.

Reporter: Habtamu H./Giyorgis
Photographer; F**d Ahmed
Haramaya University Public and International Relations Directorate

Address

Haramaya
Bate
138

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haramaya University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Haramaya University:

Share

Our Story

Well Come To Haramaya University Official page

Historical Background of the University Haramaya University has gone through a series of transformations since its establishment as a higher learning institution. The agreement signed between the Imperial Ethiopian Government and the Government of the United States of America on May 15,1952 laid the foundations for the establishment of Jimma Agricultural and Technical School and the Imperial College of Agricultural and Mechanical Arts (IECAMA). The Agreement between the Government of Ethiopia and the Technical Cooperation Administration of the Government of the United States of America, signed on May 16, 1952, gave the mandate to Oklahoma State University to establish and operate the College, conduct a nationwide system of Agricultural Extension and set up an agricultural research and experimental station. Based on the Emperor’s wish, it was decided to establish the College at its current location at Haramaya. Later on, the agreement signed between the United States Department of States and the Imperial Government provided the basis for the operation of Jimma Agricultural and Technical School that received its first class of eighty students in October 1952. Nineteen of the students graduated on August 6, 1953 and became the first freshman students of the Imperial Ethiopian College of Agricultural and Mechanical Arts (IECAMA). The IECAMA opened its doors to its first batch of students in October 1956 senior class moved from Addis Ababa to Alemaya for their final semester. At the end of the 1956/57 academic year, eleven students completed their studies and graduated with a B.Sc. degree in General Agriculture. The training programs in Agriculture were further specialized and B.Sc. programs were introduced in Animal Sciences (1960), Plant Sciences (1960), Agricultural Engineering (1961) and Agricultural Economics (1962). Until 1963, the college was virtually dependent on Oklahoma State University, both administratively and academically; however, after 1966, when the first Ethiopian dean was appointed, the role of Americans was limited to advisory and technical support. The College became a chartered member of Addis Ababa University (the then Haile Selassie I University), following the contractual termination of Oklahoma State University in 1968. Consequently, it was named Alemaya College of Agriculture. Due to the great need of trained manpower in other areas of study, additional programs that included a diploma program in Home Economics (1967), Science Teachers’ Training Program (1978), and Continuing Education Program (1980) were launched. A major landmark in the history of the College of Agriculture was the launching of graduate study programs in the 1979/80 academic year. This laid the foundation for advanced academic and research work at the institution. When graduate studies were launched, about 29 students were enrolled to study various fields of agriculture. Another major landmark in the history of Alemaya College of Agriculture was when it was upgraded to university status on May 27, 1985, followed by the launching of the Faculty of Forestry in 1987. It was then named Alemaya University of Agriculture that produced qualified manpower in the fields of Animal Sciences, Plant Sciences, Agricultural Economics, Agricultural Engineering, Agricultural Extension and Forestry both at graduate and undergraduate levels. Moreover, in the continuing education program, diploma level training programs were delivered in Accounting and Management, in Dire Dawa and Harar centers. The university once again went through another phase of transformation during the 1995/96 academic year by launching new programs in the fields of Teacher Education and Health. The opening of the two faculties, namely the Faculty of Education and the Faculty of Health Sciences, further diversified the existing programs, and enabled the institution to become a full-fledged university that was renamed Alemaya University (AU). In the last few years, the University has witnessed tremendous expansion in terms of fields of study. In September 2002, two more faculties, namely Faculty of Law and Faculty of Business and Economics, were opened. Furthermore,Faculty of Veterinary Medicine and Faculty of Technology were initiated in 2003 and 2004, respectively to further diversify the training programs of the university. The institution was renamed Haramaya University in February 2006. The University, apart from undergraduate programs, has been highly engaged in the expansion and diversification of graduate programs. .....