Haramaya University

Haramaya University Haramaya University is one of the oldest universities in Ethiopia. It is located 5 km from Haramaya, welcome
(1)

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከምስራቅ ሐረርጌ ትምህርት ጽህፈት ቤት ጋር የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች "ስቴምን" አሰጣጥን በተመለከተ ውይይት ተካሄደየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህ...
03/01/2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከምስራቅ ሐረርጌ ትምህርት ጽህፈት ቤት ጋር የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች "ስቴምን" አሰጣጥን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ተሳትፎና ኢንዱስትሪ ትስስር ዳይሬክቶሬት በምስራቅ ሐረርጌ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች "ስቴም" ግንዛቤ ፣ አጠቃቀምና የትምህርት መርጃ አቅም ላይ በስድስት ትምህርት ቤቶች ላይ በተደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ ከዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤትና ከዩኒቨርሲቲው የሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች ጋር በዳሰሳ ጥናቱ ላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አገልግሎትና ኢንዱስትሪ ትስስር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ከማል ቃሲም እንደተናገሩት የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች "ስቴም" ለሃገር እድገት መሰረት ስለሆኑ በሃገራችን በፍጥነት እያደገ ያለውን ወጣት ለትምህርት ዓይነቶቹ ፍላጎታቸው እንዲጨምር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን የማስጠበቅ ሃላፊነቱን ለመወጣት በአካባቢው የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን የመደገፍና የማብቃት ስራ ይሰራል ብለዋል፡፡

የምስራቅ ሐረርጌ ትምህርት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱረዛቅ ኢብራሂም በበኩላቸው እስካሁን በራሳቸው ውስንነት ምክንያት በትምህርቱ ዘርፍ ከዩኒቨርሲቲው መጠቀም ያለባቸውን ያክል እንዳልተጠቀሙና የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ወደ ዩኒቨርሲቲው መምጣትና ድጋፍ መጠየቅ ሲገባው የኒቨርሲቲው ወደ ዞኑ መጥቶ የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች ስቴምን በተመለከተ ያሉ ችግሮችን አጥንቶ ለውይይት መጋበዙ የሚደነቅ መሆኑንና በጥናቱ የተለዩት ድክመቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ትክክለኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ወደፊት የትምህርት ቤቶቹን የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች "ስቴም" አሰጣጥ ለማሻሻል ግብዓትና የመምህራንን ክህሎት ውስንነት ለማሻሻል ከዩኒቨርሲቲው ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ አቶ አብዱረዛቅ ገልጸዋል፡፡


የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ ኢንጅነሪንግና ሒሳብ ትምህርቶች "ስቴም" ማዕከል አስተባባሪ ዶ/ር ሄኖክ ደሳለኝ የምክክር መድረኩ አስመልክተው ሲናገሩም በምስራቅ ሐረርጌ በስድስት ትምህርት ቤቶች ላይ የተደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናትና ውስንነቶችን በጋራ መፍታት በሚቻልባቸው ሁኔታዎችና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ለመተግበር ከዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ጋር ለመመካከር የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተያዘውን ሃገራዊ አቅጣጫ በምስራቅ ሃረርጌ ዞን እንዲተገበር ዩኒቨርሲቲው እገዛ እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በድሬዳዋና አካባቢው በንብ ማነብ ስራ ለተሰማሩ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠበድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚተገበረው ሰንካሳ "SUNCASA" ፕሮጀክት የንብ ሀብትን በሚገባ ጥቅም ላይ ለማዋ...
02/01/2026

በድሬዳዋና አካባቢው በንብ ማነብ ስራ ለተሰማሩ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚተገበረው ሰንካሳ "SUNCASA" ፕሮጀክት የንብ ሀብትን በሚገባ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የድሬዳዋ አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ አስተዳደር በትብብር የንብ ሐብትን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያስችል መመሪያ ላይ ለግብርና ፣ ፅዳትና ውበት እና ለንብ ማነብ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና በሐረር ከተማ ሰጡ።

የድሬዳዋ አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ አስተዳደር ኃላፊ አቶ አብዱ መሀመድ የሰንካሳ "SUNCASA" ፕሮጀክት ለአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች ተፈጥሯዊ ምላሽ መስጠት በሚል መርህ በድሬዳዋ ከተማ አሰተዳደር የተለያዩ አረንጓዴ ልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ሰልጣኞች በአካባቢው ያለውን ምቹ ሁኔታ መሰረት በማድረግ የንብ ማነብ ስራ ላይ ማህበረሰባችን በስፋት ተጠቃሚ እንዲሆን በማገዝ የድርሻውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የ "SUNCASA" ፕሮጀክት ቴክኒካል ኃላፊ ዶ/ር አስፋው ከበደ በፕሮጀክቱ ተፈጥሯዊ የአካባቢ እንክብካቤ ልማት ስራዎች ውስጥ የንብ ማነብ ስራን ማስፋፋት አንዱ በመሆኑ በአካባቢው ያለውን የንብ ሀብት የበለጠ ጥቅም እንዲሰጥ ከስልጠና ባለፈ የንብ ቀፎዎችን ጨምሮ ሌሎች ግብአቶችን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

የተራቆቱ ቦታዎችን መልሶ ማልማት ፣ የጎርፍ መከላከል ፣ የደን ልማት እና በከተማዋ ፓርክ የመገንባት ስራዎች እያከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሰልጣኞች በበኩላቸው በአካባቢያችን የንብ ሀብትን ተጠቅመን አርአያ ሆነን አርሶአደሩን እና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል ስልጠናው ጥሩ ግንዛቤ ያገኘንበት ነው ብለዋል።

በሀገራችን ከፍተኛ የንብ ሀብት ቢኖርም ሙያዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ችግሮች በመኖራቸው የሚጠበቀውን ያህል ውጤት እየተገኘበት ባለመሆኑ ይህንን ችግር በመቅረፍ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የአቅም ግንባታ ስራዎች አስፈላጊ ናቸው ሲሉ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ መምህር የሆኑት አቶ ፈይሳ ሁንዴሳ በስልጠናው ላይ ተናግረዋል።

በታደለ ጥላሁን
ታህሳስ 24/2018ዓ.ም

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህግ ኮሌጅ በሐረሪ ክልልና በምስራቅ ሐረርጌ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ማረሚያ ቤቶች የህግ ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሄደየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህግ ኮሌጅ በሐረሪ ክልልና በ...
01/01/2026

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህግ ኮሌጅ በሐረሪ ክልልና በምስራቅ ሐረርጌ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ማረሚያ ቤቶች የህግ ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሄደ

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህግ ኮሌጅ በሐረሪ ክልልና በምስራቅ ሐረርጌ ስር በሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ማረሚያ ቤቶች በመገኘት የሴቶችንና ህጻናትን የተመለከተ የህግ ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ህግ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ሪቻርድ ዊንትዘል ዘመቻውን አስመልክተው እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው በምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች፣ በሐረሪ ክልልና ማያ ከተማ አርባ ሁለት ቢሮዎችን ከፍቶ የህግ ባለሙያዎችን በመቅጠር ነጻ የህግ ማማከርና ለአቅመ ደካሞች ጥብቅና በመቆም ያለፉትን አስራ አምስት ዓመታት በነጻ እያገለገለ ይገኛል፡፡

ነጻ ድጋፍ ለፍትህ የሚለውን መርህ በመከተል ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንና የህግ ኮሌጁም የነጻ ህግ አገልግሎት ስራዎችን መደገፊያ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ገንዘብ በማምጣት እየሰራ እንደሚገኝ ዶ/ር ሪቻርድ ገልጸዋል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህግ ኮሌጅ ንድፈ ሃሳብን ከተግባር ጋር በማዛመድ በትጉህ መምህራኖቹ ውጤታማ ተማሪዎችን በማፍራት የሚታወቅና ተማሪዎቹን ለማህበረሰቡ በነፃ የህግ አገልግሎት በመስጠት ተሳታፊ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

የዚህ ዘመቻ አላማም የህግ ታራሚዎችና ተማሪዎች መብቶቻቸውንና ግዴታዎቻቸው በመለየት ከመብቶቻቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑና ግዴታዎቻቸውንም በአግባቡ እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን ዶክተር ሪቻርድ ጠቁመው ፕሮግራሙ በዩኒቨርሲቲውና ከውጭ ሃገራት በሚገኝ ፕሮጀክት ገንዘብ እንደሚደገፍ የሚደገፍ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ህግ ኮሌጅ መምህርና የነጻ ህግ ድጋፍ አገልግሎትና የፕሮጀክቶች አስተባባሪ አቶ ጫላ ዩዬ ዘመቻውን አስመልክትው ሲናገሩ ኮሌጁ የህግ ተማሪዎችን በማሳተፍ የማህበረሰብ አገልግሎት እንደሚሰጥና ይህም ተማሪዎቹ በንድፈ ሃሳብ የተማሩትን በተግባር እንዲተገብሩና እንዲማሩበት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘም የማህበረሰብ ሃላፊነትን ለመወጣት ተማሪዎችን በተለያዩ ትምህርት ቤቶችና ማረሚያ ቤቶች በመመደብ የሴቶችና ህጻናት እንዲሁም የተማሪዎች መብትና ግዴታዎችን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ቅስቀሳ በትምህርት ቤቶች እና የታራሚዎችን የይግባኝ መብትና ሌሎችን መብቶቻቸውንና ግዴታቸው ለይተው በማወቅ በአግባቡ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ዘመቻው መከናወኑን አብራርተዋል፡፡

ዘመቻውም መጀመሪያ ዙር መሆኑንና ወደፊትም ቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚከናወን አክለው ገልጸዋል፡፡

የዘመቻው ስራው እየተከናወነ የሚገኘው የኢትዮጵያን የፍትህ አሰራርን ለመደገፍ ከአውሮፓ ህብረት ዩ.ኤን ኦዲ ሲ በተገኝ የገንዘብ ድጋፍ መሆኑን እና በሀረር ኤስ ኦ ኤስ ፣ ሀረር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ ቤተልሄም ፣ አቦከር እና ሆፕ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መከናወኑንና በምስራቅ ሃረርጌና የሀረሪ ክልል ማረሚያ ቤቶችም እንደተካሄደ አቶ ጫላ አብራርተዋል፡፡

የሐረር ቤተልሄም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ጌታቸው ተፈራ እንደተናገሩት በትምህርት ቤታቸው የተከናወነው የህግ ግንዛቤ መፍጠሪያ ትምህርት ለተማሪዎች መብቶቻቸውንና ግዴታዎቻቸውን አውቀው እንዲንቀሳቀሱ እንደሚያደርግና ይሄም ሰላማዊና ውጤታማ የመማር-ማስተማር ስራን ለማከናወን እንደሚያግዝ ገልጸዋል።


የሐረር ቤተልሄም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ረድኤት ጌቱ መሰል የህግ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች ተማሪዎች መብቶቻቸውንና ግዴታቸውን ለይተው እንዲንቀሳቀሱ ስለሚያግዙ ቀጣይነት ኖሯቸው ቢሰጡ መልካም ነው ብላለች፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈር፦ ቴዎድሮስ ሊሻን

01/01/2026
01/01/2026
የምርምር ጽሁፍ አጻጻፍና ህትመትን የተመለከተ ስልጠና ተሰጠሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮ ሳይንስና ስነቀመር ኮሌጅ ስር ለሚገኙ ጀማሪ ተመራማሪዎችና የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች በሳይንሳዊ ጽሁፍ አዘ...
01/01/2026

የምርምር ጽሁፍ አጻጻፍና ህትመትን የተመለከተ ስልጠና ተሰጠ

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮ ሳይንስና ስነቀመር ኮሌጅ ስር ለሚገኙ ጀማሪ ተመራማሪዎችና የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች በሳይንሳዊ ጽሁፍ አዘገጃጀትና የምርምር ጽሁፍ ህትመት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የሶስት ቀን ስልጠና ለ38 ሰልጣኞች ሰጥቷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የምርምር ስራዎች ዳይሬክተር ዶ/ር ደርባቸው በቃና በስልጠው መክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ከሚሰሩት የምርምር ስራዎች ውስጥ ለህትመት የሚበቁት ጥቂቶች መሆናቸውንና ለዚህም የተለያዩ ምክንያቶች ቢቀርቡም በተለይ ጀማሪና መካከለኛ ተመራማሪዎች ሳይንሳዊ የምርምር ጽሁፍ አጻጻፍን በአግባቡ አለመረዳት ብዙ ስራዎች ለህትመት እንዳይቀርቡ ምክንያት መሆኑን በዳሰሳ ጥናት መለየቱን ተናግረዋል፡፡

ይህንን ችግር ለማቃለል ተመራማሪዎች ያለባቸውን ክፍተት ለመሙላት ስልጠናው መዘጋጀቱንና የሚሰሯቸውን የምርምር ስራዎች ማሳተም እንዲችሉ ለማገዝ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

ስልጠናው ብዙ የምርምር ስራዎች እንዲታተሙና ተመራማሪዎችም ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያግዝ ፣ የዩኒቨርሲቲውንም የመታየት መጠን እንዲጨምር የሚያግዝ መሆኑን ዶ/ር ደርባቸው ተናግረዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የምርምር ህትመትና ስርጭት አስተባባሪ ዶ/ር ዘውዱ በዙ እንደገለጹት ስልጠናው በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ለሚሰሩ ጀማሪና መካከለኛ ተመራማሪዎች እንዲሁም ለድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የተሰጠ መሆኑንና በሳይንሳዊ የምርምር ጽሁፍ አጻጻፍ ላይ ያለውን ክፍተት በመሙላት የምርምር ጽሁፎችን በታዋቂ የምርምር ጆርናሎች ላይ የማሳተም ምጣኔን ከፍ ለማድረግ ስልጠናው ተሰጥቷል ብለዋል፡፡

ስልጠናው ተግባር ተኮር በሆነ መልኩ መሰጠቱንና ሰልጣኞች በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ የምርምር ጽሁፍ አዘጋጅተው እንዲያሳትሙ አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ዶ/ር ዘውዱ ተናግረዋል፡፡

የስነህይወት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም ከስልጠናው አሰልጣኞች አንዱ ዶ/ር አንዳርጌ ዘላለም እንደገለጹት ከዚህ በፊት ሳይንሳዊ የምርምር ጽሁፍ አዘገጃጀትና ህትመትን የተመለከተ ጠቃሚ ተግባር ተኮር የሆነ የአሰልጣኞች ስልጠና መውሰዳቸውንና አሁን ደግሞ የሰለጠኑትን ስልጠና አውድ በማስተካከል ለጀማሪና መካከለኛ ተመራማሪዎች እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው ሳይንሳዊ የምርምር ጽሁፍ አጻጻፍ ፣ አሳታሚ ድርጅቶችን ማፈላለግና ማሳተም እንደሚቻል እና ከህትመት በኋላም ለተመራማሪውና ለተቋሙ ያለው ጠቀሜታ ምን እንደሆነ የሚያስገነዝብ መሆኑንና ተመራማሪዎችም የምርምር ጽሁፍ ማሳተም ማለት ለተጠቃሚ ደርሶ ውጤት እንዲያመጣ ማድረግና ራስንም ለተሻለ ሁኔታ መሸጥ ማለት መሆኑን ሊረዱ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ሰልጣኞችም በበኩላቸው የተሰሩ ስራዎች ለህትመት እንዲበቁ የሚያበረታታና ወደፊትም የተሻሉ ስራዎች እንዲሰሩ የሚያግዝ ስልጠና ስለሆነ ሳይንሳዊ የምርምር ጽሁፍ አጻጻፍን መመሪያን በመከተል ለህትመት የሚበቃ የምርምር ስራ እንደሚሰሩና ራሳቸውንም ለማሳደግ እንደሚጠቅማቸው ዶ/ር ጸጉ ኪሮስና ዘይነባ አህመድ ገልጸዋል፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈር፦ ፎአድ አህመድ

በተፋሰሱ ውስጥ ለሚኖሩ ሞዴል አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች የአፈርና ውሃ ጥበቃን የተመለከተ ስልጠና ተሰጠየተቀናጀ የሐረማያ ሃይቅ ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት የሃይቁን ህልውና...
01/01/2026

በተፋሰሱ ውስጥ ለሚኖሩ ሞዴል አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች የአፈርና ውሃ ጥበቃን የተመለከተ ስልጠና ተሰጠ

የተቀናጀ የሐረማያ ሃይቅ ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት የሃይቁን ህልውናና ጽዳት ለማስጠበቅ በተግባር የታገዙ ስልጠናዎችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን የአሁኑ ስልጠናም በተፋሰሱ ውስጥ ለሚኖሩ ሰባ ሞዴል አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ የአፈርን ለምነት እንዴት መጠበቅና የመሬት መሸርሸርን ተከላክለው ምርታማ መሆን እንደሚችሉ ስልጠና ተሰጥቷል።

ከዚህም በተጨማሪ ወደ ሃይቁ የሚገባውን ደለል በመቀነስ ሃይቁ በደለል እንዳይሞላና የመስኖ ውሃን ከብክነት በጸዳ መልኩ እንዴት መጠቀም እንደሚቻሉ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የተቀናጀ የሐረማያ ሃይቅ ተፋሰስ ልማት ፕሮጅክት አስተባባሪ አቶ ዲኔ ረሺድ እንደገለጹት ስልጠና የተሰጠው ሳይንሳዊ የአፈር ለምነትና የመስኖ ውሃ አጠቃቀምን ተረድተው ለሌሎች አርሶ አደሮችም ግንዛቤ እንዲያስጨብጡ በማሰብ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ የሚከናወነው ሃገራዊ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ በሳይንሳዊ እውቀት ላይ ተመስርቶ የእርከንና የመስኖ ስራዎችን እንዲያከናውኑና የሃይቁንም በደለል የመሞላትና በጎርፍ አማካኝነት የሚገቡ በካይ ቆሻሻዎችን በመከላከል ለሃይቁ በጎ አበርክቶ እንደኖራቸው ለማገዝ ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን አቶ ዲኔ ተናግረዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊ አርሶ አደሮች በበኩላቸው ስልጠናውን የሚያከናውኑትን የአፈር ጥበቃ ፣ የእርከን ስራና የመስኖ ስራ ከልማዳዊ አሰራር በተሻለ በሳይንሳዊ መልኩ እንዴት መስራት እንደሚችሉ ፣ የመሬታቸውን ለምነትና የመስኖ ውሃን በቁጠባ ተጠቅመው ምርታማነታቸውን እንዴት ማሳደግ እንደሚችሉ ግንዛቤ መጨበጣቸውን ገልጸዋል፡፡

ዘጋቢ፡ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈር፡ ፉዓድ አህመድ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

  for All Academic Staff and PhD students of HUJoin us on Friday, January 2, 2026, at 9:00 AM (local time) in Afran Kall...
31/12/2025

for All Academic Staff and PhD students of HU

Join us on Friday, January 2, 2026, at 9:00 AM (local time) in Afran Kallo Hall for a brief (30-60 minute) orientation and registration session on HU's subscribed SPIN database, hosted by the Grant Management Directorate.

is SPIN?

SPIN (Sponsored Programs Information Network) is the world's largest database of sponsored funding opportunities, featuring over 40,000 opportunities from more than 10,000 public, non-profit, and private sponsors worldwide.

Benefits for Registered Users:

- Set up and save personalized search preferences
- Receive email notifications for new opportunities
- Organize, export, and track funding searches

This is a golden opportunity for HU academic staff seeking external funding to access the premier global database, completely free with your institutional email (HU covers the subscription!).

We'll cover a basic overview of SPIN, hands-on navigation tips, and step-by-step registration for individual accounts.

't miss this privilege of HU membership, elevate your research and career! See you Friday morning.

.B

institutional email is a requirement for registration

Grant Management Directorate

Professor Gebisa Ejeta Inspires African Youth to Drive Continental Transformation Through Education and InnovationHarama...
31/12/2025

Professor Gebisa Ejeta Inspires African Youth to Drive Continental Transformation Through Education and Innovation

Haramaya University proudly hosted the renowned plant breeder and World Food Prize laureate, Professor Gebisa Ejeta, who delivered an inspiring lecture encouraging African youth to embrace education, innovation, and creativity as the driving forces behind Africa’s transformation.

Speaking on the theme “African Youth for Africa’s Transformation,” Professor Ejeta emphasized that the continent’s future rests on the shoulders of its young people. “African youth must educate themselves to claim their rightful role in Africa’s transformation,” he declared, underscoring the importance of human capital development.

Professor Gebisa highlighted that Africa’s growth and prosperity depend on harnessing creativity, innovation, and managerial skills. He pointed to global examples, including the United States, Europe, the Asian Tigers, and BRICS nations, as economies propelled by science, technology, and innovation.

“Africa’s youth, numbering over 400 million aged 15–35, must be empowered through education and equipped with technology and creativity to solve both local and global challenges,” he stated.

Drawing from his personal experiences, Professor Gebisa encouraged students to pursue excellence through discipline and hard work. He shared his formula for success from his time at Haramaya University: “I focused on my studies, managed my time effectively, took on extra jobs at the university, and earned additional income. I also played basketball for recreation. Overall, I used my time productively to achieve results.”

The event began with remarks from Dr. Jemal Yousuf, President of Haramaya University, who expressed deep appreciation: “Our distinguished Professor Gebisa Ejeta generously shares his life lessons with our community to inspire Africa’s transformation. We thank him sincerely.”

In recognition of his contributions, Haramaya University honored Professor Gebisa by naming its library after him. During his visit on December 30, 2025, Professor Gebisa and his family pledged to enhance the library’s facilities. “This library is crucial for producing qualified citizens. Together with my family, we will work to improve it,” he affirmed.

Mr. Tilahun Shiferaw, the Director of the University Library and Information Service, announced the launch of a digital exhibit that highlights Professor Ejeta's impressive life and career achievements. The exhibit features over 260 publications, prestigious awards, including honors from the World Food Program, a former U.S. President, and Purdue University, as well as a rich collection of photographs that document his journey.

Reporter: Demoz Yakob
Photographers: Fuad Ahmed, Behailu Girma, and Theowodros Lishan

የሀዘን መግለጫበሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ተቋም የምግብ ሳይንስ እና ድህረ-ምር ምህንድስና ትምህርት ክፍል ባልደረባ የነበሩት አቶ ሸዋንግዛው ተከተል አናሞ ያደረባቸውን ህመም በህክምና ሲረ...
31/12/2025

የሀዘን መግለጫ

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ተቋም የምግብ ሳይንስ እና ድህረ-ምር ምህንድስና ትምህርት ክፍል ባልደረባ የነበሩት አቶ ሸዋንግዛው ተከተል አናሞ ያደረባቸውን ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

አቶ ሸዋንግዛው ተከተል አናሞ መስከረም 11/1977 ዓ.ም በምስራቅ ሸዋ መተሀራ ከተማ ተወልደው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በመርቲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በመርቲ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡ በመቀጠልም በ1998 ዓ.ም ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ በኬሚስትሪ ላብራቶሪ በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡

በዲፕሎማ ከተመረቁ በኋላ በወላይታ መምሕራን ትምህርት ኮሌጅ ለ1 ዓመት ተኩል ካገለገሉ በኋላ በ2001 ዓ.ም ሐረማያ ዪኒቨርሲቲ በምግብ ሳይንስና ድሕረ-ምርት ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ተቀጥረው ስራ ጀምረዋል፡፡

ስራቸውን እየሰሩ ትምህርታቸውን በመቀጠል በ2007 ዓ.ም በምግብ ሳይንስና ድሕረ-ምርት ቴክኖሎጂ በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በ2016 ዓ.ም ደግሞ በተመሳሳይ በምግብ ሳይንስ ቴክኖሎጂ በሁለተኛ ዲግሪ ተመርቀዋል።

አቶ ሸዋንግዛው ተከተል እስከ እለተ ሞታቸው ድረስ በዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ በአጠቃላይ ለ17 ዓመት አገልግለዋል። አቶ ሸዋንግዛው ተከተል ትናንት ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ቤተሰቦቹ በሚኖሩበት ዱራሜ ከተማ ስርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር በአቶ ሸዋንግዛው ተከተል አናሞ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና በአጠቃላይ ለዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ መጽናናትን ይመኛል፡፡

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም

Address

Haramaya
Bate
138

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haramaya University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Haramaya University:

Share

Our Story

Well Come To Haramaya University Official page

Historical Background of the University Haramaya University has gone through a series of transformations since its establishment as a higher learning institution. The agreement signed between the Imperial Ethiopian Government and the Government of the United States of America on May 15,1952 laid the foundations for the establishment of Jimma Agricultural and Technical School and the Imperial College of Agricultural and Mechanical Arts (IECAMA). The Agreement between the Government of Ethiopia and the Technical Cooperation Administration of the Government of the United States of America, signed on May 16, 1952, gave the mandate to Oklahoma State University to establish and operate the College, conduct a nationwide system of Agricultural Extension and set up an agricultural research and experimental station. Based on the Emperor’s wish, it was decided to establish the College at its current location at Haramaya. Later on, the agreement signed between the United States Department of States and the Imperial Government provided the basis for the operation of Jimma Agricultural and Technical School that received its first class of eighty students in October 1952. Nineteen of the students graduated on August 6, 1953 and became the first freshman students of the Imperial Ethiopian College of Agricultural and Mechanical Arts (IECAMA). The IECAMA opened its doors to its first batch of students in October 1956 senior class moved from Addis Ababa to Alemaya for their final semester. At the end of the 1956/57 academic year, eleven students completed their studies and graduated with a B.Sc. degree in General Agriculture. The training programs in Agriculture were further specialized and B.Sc. programs were introduced in Animal Sciences (1960), Plant Sciences (1960), Agricultural Engineering (1961) and Agricultural Economics (1962). Until 1963, the college was virtually dependent on Oklahoma State University, both administratively and academically; however, after 1966, when the first Ethiopian dean was appointed, the role of Americans was limited to advisory and technical support. The College became a chartered member of Addis Ababa University (the then Haile Selassie I University), following the contractual termination of Oklahoma State University in 1968. Consequently, it was named Alemaya College of Agriculture. Due to the great need of trained manpower in other areas of study, additional programs that included a diploma program in Home Economics (1967), Science Teachers’ Training Program (1978), and Continuing Education Program (1980) were launched. A major landmark in the history of the College of Agriculture was the launching of graduate study programs in the 1979/80 academic year. This laid the foundation for advanced academic and research work at the institution. When graduate studies were launched, about 29 students were enrolled to study various fields of agriculture. Another major landmark in the history of Alemaya College of Agriculture was when it was upgraded to university status on May 27, 1985, followed by the launching of the Faculty of Forestry in 1987. It was then named Alemaya University of Agriculture that produced qualified manpower in the fields of Animal Sciences, Plant Sciences, Agricultural Economics, Agricultural Engineering, Agricultural Extension and Forestry both at graduate and undergraduate levels. Moreover, in the continuing education program, diploma level training programs were delivered in Accounting and Management, in Dire Dawa and Harar centers. The university once again went through another phase of transformation during the 1995/96 academic year by launching new programs in the fields of Teacher Education and Health. The opening of the two faculties, namely the Faculty of Education and the Faculty of Health Sciences, further diversified the existing programs, and enabled the institution to become a full-fledged university that was renamed Alemaya University (AU). In the last few years, the University has witnessed tremendous expansion in terms of fields of study. In September 2002, two more faculties, namely Faculty of Law and Faculty of Business and Economics, were opened. Furthermore,Faculty of Veterinary Medicine and Faculty of Technology were initiated in 2003 and 2004, respectively to further diversify the training programs of the university. The institution was renamed Haramaya University in February 2006. The University, apart from undergraduate programs, has been highly engaged in the expansion and diversification of graduate programs. .....