Haramaya University

Haramaya University Haramaya University is one of the oldest universities in Ethiopia. It is located 5 km from Haramaya, welcome
(1)

16/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች



Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

16/11/2025
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን ምክንያት በማድረግ የመዝናኛ ዝግጅት ቀረበየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ከተማሪዎች አደረጃጀት...
16/11/2025

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን ምክንያት በማድረግ የመዝናኛ ዝግጅት ቀረበ

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ከተማሪዎች አደረጃጀትና ከበዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ጋር በመተባበር በዓሉን አስመልክቶ የመዝናኛ ዝግጅቱን ቅዳሜ ህዳር 6/2018 ዓ.ም በሙዚቀኛ ሀጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ መናፈሻ ውስጥ አካሂደዋል።

የሴቶች ፣ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ ከዲጃ አብዱልቃድር 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለአቅመ ደካማዎች ድጋፍ የማሰባሰብ ስራ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህብረተሰብ ሳይንስ ኮሌጅ ዲንና የመርሐ ግብሩ አስተባባሪ ዶክተር መሐመድ ሐሰን እንዳብራሩት የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በየዓመቱ ህዳር 29 የሚከበር ፣ ጥያቄውም ለዘመናት በተማሪዎች ጥያቄ ሆኖ የቀረበና መልስ በማግኘቱ በየዓመቱ እየተከበረ መሆኑን አብራርተዋል።

ዘንድሮም እስከ ኅዳር 21/2018 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በተለያዩ መርሀ ግብሮች በዓሉን በማክበር ህገ መንግስቱን የማስተዋወቅ ስራ እንደሚሰራ ዶክተር መሐመድ አብራርተዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ተወካይ አቶ ሙክታር ዳውድ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው የሚመጡ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ብቻ ሳይሆን የአካባቢውንም ማህበረሰብ ጭምር መርጠው ስለሚመጡ የአካባቢውን ባህል በማወቅና በማስተዋወቅ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ እያበረከቱ ነው ብለዋል።

ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው ከተለያዩ ብሔረሰቦች ከመጡ ተማሪዎች ጋር ልምድ በመለዋወጥ በመቀራረብ የሀገራቸውን ነባራዊ ሁኔታ እንዲማማሩ አቶ ሙክታር ጥሪ አቅርበዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት የአደረጃጀት ቦርድ ሰብሳቢ ተማሪ ሚደቅሳ ደጀኔ የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች የሐረማያ ሀይቅንና የዩኒቨርሲቲውን ጊቢ በማፅዳት ፣ በደም የመለገስ ፣ በበጎ አድራጎት ስራዎችና የመዝናኛ ዝግጅቶች ላይ ተማሪዎች በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግሯል።

በተዘጋጀው የመዝናኛ መድረክ የተለያዩ ስነጽሁፎች ፣ ውዝዋዜዎችና መነባንብ ቀርቧል።

ዘጋቢ ፦ ሐብታሙ ኃብተጊዮርጊስ
ፎቶግራፈር፦ ፎአድ አህመ

16/11/2025
ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በእረፍት ቀናት የሳ ይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ እንግሊዘኛና የሒሳብ ትምህርት ማጠናከሪያ (STEM) ስልጠና መስጠት ተጀመረየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አ...
15/11/2025

ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በእረፍት ቀናት የሳ ይንስ ፣ ቴክኖሎጂ ፣ እንግሊዘኛና የሒሳብ ትምህርት ማጠናከሪያ (STEM) ስልጠና መስጠት ተጀመረ

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና ኢንደስትሪ ትስስር ዳይሬክቶሬት በዩኒቨርሲቲው አካባቢ ከሚገኙ አራት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 100 ተማሪዎች በሳይንስ ፣ በቴክኖሎጂ ፣ በኢንጂነሪነግና በሂሳብ ትምህርቶች ላይ የተመሰረተ ተግባር ተኮር የአምስት ሳምንት ስልጠና ዛሬ መስጠት ጀምሯል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የስቴም ማዕከል አስተባባሪ ዶ/ር ሄኖክ ደሳለኝ እንደገለጹት ስልጠናው የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ለሳይንስ ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ፍላጎትና ግንዛቤ ከፍ ለማድረግ ከንድፈ በተጨማሪ በቤተ ሙከራዎች የተደገፈ ተግባር ተኮር ስልጠና እንዲያገኙ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡

ስልጠናው በሳምንት ሁለት ቀን ቅዳሜና እሁድ ለአምስት ሳምንታት እንደሚሰጥ ዶ/ር ሄኖክ ገልጸዋል፡፡

ስልጠናውን የዩኒቨርሲቲው ስቴም ማዕክል በዘርፉ ከሚሰራው ስቴም ሲነርጂ (STEM SYNERGY Inc) ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር የሚሰጥ መሆኑን ዶ/ር ሄኖክ ተናግረዋል፡፡

ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በበኩላቸው ለሳይንስ ዘርፍ ያላቸውን ፍላጎትና እውቀት በቤተ ሙከራ በተግባር በመማር ለማሳደግ እንደመጡና ከስልጠናውም ተግባራዊ እውቀት እናገኛለን ብለው እንደሚጠብቁ ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈር፦ ቴዎድሮስ ሊሻን
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ኅዳር 6/2018 ዓ.ም

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በተለያዩ መርሐግብሮች እየተከበረ ነው በዓሉ ደም በመለገስ ፣ አካባቢን በማፅዳት ፣ ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ በማሰባሰብና በሌሎ...
15/11/2025

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በተለያዩ መርሐግብሮች እየተከበረ ነው

በዓሉ ደም በመለገስ ፣ አካባቢን በማፅዳት ፣ ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ በማሰባሰብና በሌሎች መርሐግብሮች እስከ ህዳር 20 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እየተከበረ ይገኛል።

ህዳር 20 በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የነበረው የበዓል አከባበር በፓናል ውይይት የሚጠናቀቅ ይሆናል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ ዲንና የበዓሉ አስተባባሪ ዶክተር መሐመድ ሐሰን እንዳብራሩት የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል የህዝቦችን እኩልነት የሚያንፀባርቅ
መሆኑንና በዛሬው ዕለትም ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የተሳተፉበት የፅዳት ዘመቻ መከናወኑን ገልፃዋል።

በፅዳት ዘመቻው የተሳተፉት የተማሪዎች አደረጃጀት ቦርድ ሰብሳቢ ተማሪ ሚደቅሳ ደጀኔና በተማሪዎች ህብረት ስር የማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ ተማሪ እፁብ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን ምክንያት በማድረግ የተካሄደው የፅዳት ዘመቻ አካባቢን ከመጠበቅ ባሻገር ተማሪዎች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና እንዲቀራረቡ ያግዛል ብለዋል።

ዘጋቢ ፦ ሐብታሙ ኃብተጊዮርጊስ
ፎቶግራፈር፦ ፎአድ አህመድ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ህዳር 6 ቀን 2018 ዓ/ም

የፀረሙስና ስራዎችን የተመለከተ የተማሪዎች ውድድር ተደረገበሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የተማሪዎች የፀረሙስና የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎ...
15/11/2025

የፀረሙስና ስራዎችን የተመለከተ የተማሪዎች ውድድር ተደረገ

በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የተማሪዎች የፀረሙስና የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለመለየት የጥያቄና መልስ ውድድሩ መዘጋጀቱ ተገልጿል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የፀረ ሙስናና ስነምግባር ዳይሬክቶሬት ባዘጋጀው የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር ላይ አስር የዩኒቨርሲቲው የፀረሙስናና ስነምግባር ክበብ አባል ተማሪዎች ተሳትፈዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የፀረ ሙስናና ስነምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘላለም ደሳለኝ እንዳብራሩት በተማሪዎች መካከል የተካሄደው የጥያቄና መልስ ውድድር አላማ በሐገር አቀፍ ደረጃ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል በሚዘጋጀው ውድድር ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎችን ለመለየትና ለማዘጋጀት መሆኑን አብራርተዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት የህግ ተማሪና የውድድሩ አሸናፊ ተማሪ ሶሪቲ ሶሬሳ እንዳለችው ውድድሩ ስለሙስና ያለኝን ግንዛቤ ያሳደኩበትና በቀጣይ በሐገር አቀፍ ደረጃ ለሚኖረው ውድድር አስፈላጊውን ዝግጅት ያደረኩበት ነው ተብላለች።

በተካሄደው የጥያቄና መልስ ውድድር
ሶሬቲ ሶሬሳ ፣ ሁሲን ሐሰን እና አብዱከሪም ሐሰን ከአንድ እስከ ሶስተኛ በመውጣት አሸናፊ ሆነዋል።

ዘጋቢ ፦ ሐብታሙ ኃብተጊዮርጊስ
ፎቶግራፈር፦ ቴዎድሮስ ሊሻን
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ህዳር 6 ቀን 2018 ዓ/ም

Biotech for Africa Symposium Spotlights Emerging Solutions for Food SafetyEgerton University in Kenya hosted the Biotech...
15/11/2025

Biotech for Africa Symposium Spotlights Emerging Solutions for Food Safety

Egerton University in Kenya hosted the Biotech for Africa Symposium from November 12–14, 2025, bringing together scientists, policymakers, and development partners to explore advancements in agricultural biotechnology across the continent.

Dr. Abdi Mohammed, Vice President for Administration and Development at Haramaya University and an active researcher in food safety, represented the institution at the event.

Dr Abdi delivered a presentation titled “Mycotoxins in the Ethiopian Food System: Current Burden and Emerging Biotechnology as a Solution,” highlighting the scale of mycotoxin contamination in Ethiopia and outlining biotechnology-driven interventions with the potential to reduce risks across the food value chain.

The symposium was funded by the USDA Agricultural Research Service (USDA–ARS) through Florida Agricultural and Mechanical University (FAMU), USA.

It is part of the broader Biotechnology Advocacy Project, “Establishing Sustainable Networks of Next-Generation Change Agents in Agricultural Biotechnology and Biosafety to Enhance Knowledge and Awareness in Africa,” which aims to build capacity and strengthen regional collaboration in biotechnology and biosafety.

Haramaya University Public & International Relations Directorate

ተማሪዎች ያሰቡትን ዕቅድ ለማሳካት ለጊዜ አጠቃቀማቸው ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ተባለለአዲስ ገቢ ልዩፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችና ለሴት ተማሪዎች ልምድ የሚቀስሙበት መድረክ ተካሂዷል። የሐረማያ ዩኒ...
14/11/2025

ተማሪዎች ያሰቡትን ዕቅድ ለማሳካት ለጊዜ አጠቃቀማቸው ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ተባለ

ለአዲስ ገቢ ልዩፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችና ለሴት ተማሪዎች ልምድ የሚቀስሙበት መድረክ ተካሂዷል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት በዘንድሮው ዓመት አዲስ ገቢ ለሆኑ ልዩ ፍላጎት ላላቸውና ለሴት ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መድረክ አዘጋጅቶ የልምድ ልውውጥ መድረክና የዳይሬክቶሬቱን ስራዎች የሚያስተዋውቅ መድረክ እዘጋጅቷል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ፣ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ከድጃ አብዱልቃድር እንደገለጹት አዲስ ገቢ ልዩ ፍላጎት ያላቸውና ሴት ተማሪዎች አብዛኞቹ ለግቢ ህይወት አዲስ ስለሆኑ ከታላላቆቻቸውና ለግቢ ህይወት የቀደመ ልምድ ካላቸው እህቶቻቸው እንዲማሩ ለማድረግ መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

ሴት ተማሪዎች ትኩረታቸውን ትምህርት ላይ ብቻ ካደረጉና የታላላቅ ሰዎችን የህይወት ተሞክሮ በመከተል ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም በርትተው ከተማሩ ስኬታማ እንደሚሆኑ ወ/ሮ ከድጃ ገልጸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች አስፈላጊውን የትምህርት መርጃ የቁሳቁስ ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንና ተማሪዎች ከግቢ ውጭ ሲወጡ እንዳይቸገሩ በዩኒቨርሲቲው አካባቢ ለሚገኙ የመንግስትና የግል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የምልክት ቋንቋ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ወ/ሮ ከድጃ ተናግረዋል፡፡

የመድረኩ ተሳታፊ ተማሪዎች በበኩላቸው ከተካሄደው ውይይትና የልምድ ልውውጥ ለወደፊት የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የሚጠቅም ግብዓት ማግኘታቸውን ገልጸው ዩኒቨርሲቲው በተለይ ልዩፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ልዩ እንክብካቤ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ተማሪዎቹ ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ዘጋቢ፦ አወቀ አያልነህ
ፎቶግራፈሮች፦ ቴዎድሮስ ሊሻንና ፎአድ አህመድ
ኅዳር 05/2018 ዓ.ም

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን በማስመልከት የህገመንግስት ጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት እና የእንስሳት ህክምና ኮሌጅ ተማሪዎች...
14/11/2025

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን በማስመልከት የህገመንግስት ጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት እና የእንስሳት ህክምና ኮሌጅ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን በማስመልከት በዛሬው ዕለት የህገ መንግስት ጥያቄና መልስ ውድድር አከናውነዋል።

የጥያቄና መልስ ውድድሩ ባለፈው ኣምንትም በጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ውስጥ የተከናወነ ሲሆን የየካምፓሶቹ አሸናፊዎች የሚገናኙበት ውድድር ተካሂዶ አሸናፊዎቹ ተሸላሚ እንደሚሆኑ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር መሐመድ ሀሰን ተናግረዋል።

የበዓሉ ዝግጅት አካል የሆኑ የአልባሳት ድጋፍ ማሰባሰብና የፅዳት ዘመቻ ስራዎች ነገ ቅዳሜ ህዳር 6/2018 ዩኒቨርሲቲው ውስጥ የሚከናወን ሲሆን ምሽት ላይ የባህል ትርዒትም እንደሚቀርብ ዶክተር መሀመድ ተናግረዋል።

ፎቶግራፈር፦ ቴዎድሮስ ሊሻን
ህዳር 5/2018
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

  Notice To All First-Year Postgraduate StudentsWe are delighted to welcome you to Haramaya University, your new academi...
14/11/2025




Notice To All First-Year Postgraduate Students
We are delighted to welcome you to Haramaya University, your new academic home, where diversity thrives, innovation grows, and we serve each other as one family. Please take note of the following important details and registration dates for the 2025/26 academic year.

📑 Please bring your academic documents and sponsorship letter in person during registration.

📅 Online Registration Period: November 20 & 21, 2025 (Hidar 11 & 12, 2018)

⚠️ Late Registration (with Penalty): November 24 & 25, 2025 (Hidar 15 & 16, 2018)

🏠 Dormitories Open: Starting from November 15, 2025 (Hidar 6, 2018)

💬 Stay Connected: Join our official Telegram group for updates and guidance:👉 https://t.me/+NLr_kE1MnWJjYjA1

NB: The registration link will be shared after your arrival through internal notice and official Telegram group channel. Please note that the link will only work within the campus network.

We wish you a productive and inspiring postgraduate journey at Haramaya University!

14/11/2025


Address

Haramaya
Bate
138

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haramaya University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Haramaya University:

Share

Our Story

Well Come To Haramaya University Official page

Historical Background of the University Haramaya University has gone through a series of transformations since its establishment as a higher learning institution. The agreement signed between the Imperial Ethiopian Government and the Government of the United States of America on May 15,1952 laid the foundations for the establishment of Jimma Agricultural and Technical School and the Imperial College of Agricultural and Mechanical Arts (IECAMA). The Agreement between the Government of Ethiopia and the Technical Cooperation Administration of the Government of the United States of America, signed on May 16, 1952, gave the mandate to Oklahoma State University to establish and operate the College, conduct a nationwide system of Agricultural Extension and set up an agricultural research and experimental station. Based on the Emperor’s wish, it was decided to establish the College at its current location at Haramaya. Later on, the agreement signed between the United States Department of States and the Imperial Government provided the basis for the operation of Jimma Agricultural and Technical School that received its first class of eighty students in October 1952. Nineteen of the students graduated on August 6, 1953 and became the first freshman students of the Imperial Ethiopian College of Agricultural and Mechanical Arts (IECAMA). The IECAMA opened its doors to its first batch of students in October 1956 senior class moved from Addis Ababa to Alemaya for their final semester. At the end of the 1956/57 academic year, eleven students completed their studies and graduated with a B.Sc. degree in General Agriculture. The training programs in Agriculture were further specialized and B.Sc. programs were introduced in Animal Sciences (1960), Plant Sciences (1960), Agricultural Engineering (1961) and Agricultural Economics (1962). Until 1963, the college was virtually dependent on Oklahoma State University, both administratively and academically; however, after 1966, when the first Ethiopian dean was appointed, the role of Americans was limited to advisory and technical support. The College became a chartered member of Addis Ababa University (the then Haile Selassie I University), following the contractual termination of Oklahoma State University in 1968. Consequently, it was named Alemaya College of Agriculture. Due to the great need of trained manpower in other areas of study, additional programs that included a diploma program in Home Economics (1967), Science Teachers’ Training Program (1978), and Continuing Education Program (1980) were launched. A major landmark in the history of the College of Agriculture was the launching of graduate study programs in the 1979/80 academic year. This laid the foundation for advanced academic and research work at the institution. When graduate studies were launched, about 29 students were enrolled to study various fields of agriculture. Another major landmark in the history of Alemaya College of Agriculture was when it was upgraded to university status on May 27, 1985, followed by the launching of the Faculty of Forestry in 1987. It was then named Alemaya University of Agriculture that produced qualified manpower in the fields of Animal Sciences, Plant Sciences, Agricultural Economics, Agricultural Engineering, Agricultural Extension and Forestry both at graduate and undergraduate levels. Moreover, in the continuing education program, diploma level training programs were delivered in Accounting and Management, in Dire Dawa and Harar centers. The university once again went through another phase of transformation during the 1995/96 academic year by launching new programs in the fields of Teacher Education and Health. The opening of the two faculties, namely the Faculty of Education and the Faculty of Health Sciences, further diversified the existing programs, and enabled the institution to become a full-fledged university that was renamed Alemaya University (AU). In the last few years, the University has witnessed tremendous expansion in terms of fields of study. In September 2002, two more faculties, namely Faculty of Law and Faculty of Business and Economics, were opened. Furthermore,Faculty of Veterinary Medicine and Faculty of Technology were initiated in 2003 and 2004, respectively to further diversify the training programs of the university. The institution was renamed Haramaya University in February 2006. The University, apart from undergraduate programs, has been highly engaged in the expansion and diversification of graduate programs. .....